20/03/2023
"የቴክኒክ ባለሞያዎች የንድፈ ሃሳብ እና የተግባር ልምምድ ለማድረግ የሚያስችል የእውቀት ሸግግር እየተደረገ መሆኑ የድርጅታችንን የቴክኒክ አቅም ከፍ ያደርገዋል" ሲሉ የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ግዛው አለሙ የመክፈቻ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ሲያደረጉ ገልጸዋል።
በእውቀት የተደገፈ ጥገና ለአዳዲሶቹ አውቶቡሶችን ለማድረግ እና የእውቀት ሽግግር ለማድረግ የሚያሰችል ስልጠና እየሰጠ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የግብአት አቅርቦት እና የቴክኒክ ምርት አስተዳደር ዘርፍ ም/ዋ/ስራ አስኪያጅ ኢ/ር አዳነ አብደታ አብራርተዋል ።
ዘመናዊነትን ተረድተው ፈጣንና ውጤታማ የሆነ ጥገና ለማድረግ የሚያስችል ስልጠና ከሃይገር ካንፖኒ በመጡ ባለሞያዎች ለጅርጅቱ የቴክኒክ ባለሞያዎች እየተሰጠ እና የእውቀት ሽግግር አየተደረገ መሆኑ የቴክኒክ ምርት አገልግሎት ዳይሬክተርነት ዳይሬክተር አቶ እሱያውቃል መላኩ ገልፀዋል።
ዳይሬክተሩ አያይዘው እንደገለፁት ስልጠናው በዙር ለሁሉም የቴክኒክ ባለሞያዎች እንደሚሰጥና ITS ፣ ኤሌክትሪክ ፣አውቶማቲክ ትራንስሚሽን ፣ኤር ብሬክ ሲስተም ፣አንቲ ብሬክ ሎክ ሲስተም እና የመሳሰሉትን ለጥገና ግብዓት ሊሆኑ የሚችሉ የንድፈ ሃሳብና የተግባር ላይ ልምምድ እና ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን አብራርተዋል።